ወቅታዊ ዜና

በቱሪዝም ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተመዝግቧል

ሚኒስትር ሰላማዊ ካሳ የቱሪዝም ዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መመዝገቡን የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሣ አስታወቁ። የቱሪዝም ሚኒስቴር የ2018 በጀት ዓመት የዘርፉ የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በአርባ

ለበለጠ መረጃ »

የመዲናዋ ሆቴሎች ለአፍሪካ እንግዶች የኢትዮጵያን እንግዳ ተቀባይነት የሚያንጸባርቅ መሥተንግዶ

ሆቴሎች አስፈላጊውን ዝግጅት በማጠናቀቅ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ተሳታፊ እንግዶችን መቀበል ጀምረዋል አለ የአዲስ አበባ ሆቴል ባለቤቶች ማህበር፡፡ የማህበሩ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አስቴር ሰለሞን ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ የአዲስ አበባ ሆቴሎች የአፍሪካ

ለበለጠ መረጃ »

ሀገራችን በዩኔስኮ ያስመዘገበቻቸው ቅርሶች 18 ደርሰዋል – የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ

የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ “ጊፋታ” በዓል በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ድርጅት ዩኔስኮ መመዝገቡን ምክንያት በማድረግ የደስታ ማብሰሪያ መርኃ ግብር በወላይታ ሶዶ ስታዲየም ተካሂዷል። በመርኃ ግብሩ ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት

ለበለጠ መረጃ »

በቡና ቱሪዝም ላይ የሚመክር ሀገር አቀፍ ጉባኤ ተካሄደ::

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (JICA) ጋር በመተባበር ቡናን በሀገሪቱ የቱሪስት መዳረሻነት ማዕቀፍ ውስጥ ለማካተት የሚያስችል ሀገር አቀፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በጅማ ከተማ አካሂዷል። ይህ መድረክ በዋናነት የተበታተኑ የቡና

ለበለጠ መረጃ »

በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ዘርፍ እንዲሰማሩ ከኢትዮ-አሜሪካን የንግድ ምክር ቤት አባላት ብዙ ይጠበቃል፡፡

ሚኒስትሯ ከዋሽንግተን ዲ.ሲ. እና ከተለያዩ የአሜሪካን ግዛቶች የተውጣጡ የኢትዮ-አሜሪካን የንግድ ምክር ቤት አባላት በቢሯቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት እንዳሉት አሁን ያለው የኢትዮጵያ ገጽታ ለተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ምቹና ሳቢ ነው፡፡ በተለይ ባለፉት ጥቂት

ለበለጠ መረጃ »

“ከአንኮበር እስከ ሐረር በር”፦ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የ6 ከተሞች ውድድር በደብረ ብርሃን በድምቀት ተጀመረ::

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና “ከአንኮበር እስከ ሐረር በር” በሚል መሪ ቃል ሀገርን በሩጫ ለማስተዋወቅ የታቀደው የ6 ከተሞች የሩጫ ውድድር ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ በታላቅ ድምቀት ተካሂዷል። በከተማዋ

ለበለጠ መረጃ »

በቱሪዝም ዘርፍ በቅርብ ዓመታት የተሰሩ መዳረሻዎች ለአገር ገጽታ ግንባታ ከመሆንም በላይ አለም አቀፍ የቱሪዝም መዳረሻ መሆን ችለዋል

መንግስት ባለፉት ዓመታት ለቱሪዝም ዘርፉ በሰጠው ትኩረት የሀገራችንን ጸጋዎች በመረዳት በማልማት፣ በመጠበቅና በመንከባከብ በጠቅላይ ሚኒስቴር ፕሮጅክት  ብቻ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ  ለምተው በአዲስ መልክ  ለጎብኚዎች  ክፍት ሆነዋል

የቱሪዝም ዘርፍ የትኩረት መስኮች

01

የቱሪስት መዳረሻ እና መሠረተ ልማት

አዳዲስ የቱሪዝም መስህቦችን ያለማል፣ ነባር የቱሪዝም መዳረሻዎች እንዲጎለብቱ እና የቱሪዝም ምርት እና አገልግሎት በዓይነትና በመጠን እንዲያድጉ በማድረግ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያደርጋል፣ የግል ባለሃብቶችም በልማቱ እንዲሳተፉ ያበረታታል፤

02

የቱሪዘም ገበያ ልማት

የተለያዩ የቱሪዝም ባለድርሻ አካላት የሚያከናውኗቸውን የቱሪዝም ገበያ ፍለጋና ማስተዋወቅ፣ የገበያ ትስስር እና ብራንዲንግ ሥራዎችን በማቀናጀትና በመምራት የአገሪቱን የቱሪዝም ሃብቶች፣ መስህቦችና መልካም ገፅታ በውጭ ሀገርና በሀገር ውስጥ በስፋት ያስተዋውቃል፤ አዳዲስ የቱሪዝም ገበያዎችን ይፈጥራል፣ የዘርፉን የገበያ ድርሻ እንዲያድግ ያደርጋል፤

03

የቱሪስት አገልግሎቶች ልህቀት

የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ደረጃዎች ይወስናል፣ ተፈጻሚነቱን ይቆጣጠራል፤

ሥልጣኑ በግልጽ በሌላ አካል ካልተሰጠ በስተቀር ከአንድ በላይ በሆኑ ክልሎች ውስጥ አገልግሎት ለሚሰጡ ወይም ህግ በሚፈቅደው አግባብ በውጭ ባለሀብቶች ለሚካሄዱ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ፈቃድ ይሰጣል፣ ይቆጣጠራል፤

04

የተፈጥሮና ባህላዊ ሃብቶች ጥበቃና አጠቃቀም

የሀገሪቱ የተፈጥሮ ቅርሶች እንዲጠኑ፣ እንዲጠበቁና ለቱሪዝም አመቺ ሆነው እንዲለሙና ጥቅም ላይ እንዲውሉ የሚደረጉበትን ሁኔታ ያመቻቻል፤

05

ተቋማዊ አቅም ግንባታ

አመራርና ሰራተኞች የእውቀት ክህሎትና የአመለካከት ለውጥ በማምጣት፤ሚኒስቴር መ/ቤቱ የተጣለበትን ተቋማዊ ሃላፊነት በብቃት እንዲወጣ የሚያስችሉ በርካታ ሙያዊ ስልጠናዎችን ያዘጋጃል፡፡

ለተፈጥሮ ወዳድ ጎብኚዎች ይምጡ ኢትዮጵያን ይጎብኙ!