የቱሪዝም ዘርፍ የትኩረት መስኮች
01
የቱሪስት መዳረሻ እና መሠረተ ልማት
አዳዲስ የቱሪዝም መስህቦችን ያለማል፣ ነባር የቱሪዝም መዳረሻዎች እንዲጎለብቱ እና የቱሪዝም ምርት እና አገልግሎት በዓይነትና በመጠን እንዲያድጉ በማድረግ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያደርጋል፣ የግል ባለሃብቶችም በልማቱ እንዲሳተፉ ያበረታታል፤
02
የቱሪዘም ገበያ ልማት
የተለያዩ የቱሪዝም ባለድርሻ አካላት የሚያከናውኗቸውን የቱሪዝም ገበያ ፍለጋና ማስተዋወቅ፣ የገበያ ትስስር እና ብራንዲንግ ሥራዎችን በማቀናጀትና በመምራት የአገሪቱን የቱሪዝም ሃብቶች፣ መስህቦችና መልካም ገፅታ በውጭ ሀገርና በሀገር ውስጥ በስፋት ያስተዋውቃል፤ አዳዲስ የቱሪዝም ገበያዎችን ይፈጥራል፣ የዘርፉን የገበያ ድርሻ እንዲያድግ ያደርጋል፤
03
የቱሪስት አገልግሎቶች ልህቀት
የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ደረጃዎች ይወስናል፣ ተፈጻሚነቱን ይቆጣጠራል፤
ሥልጣኑ በግልጽ በሌላ አካል ካልተሰጠ በስተቀር ከአንድ በላይ በሆኑ ክልሎች ውስጥ አገልግሎት ለሚሰጡ ወይም ህግ በሚፈቅደው አግባብ በውጭ ባለሀብቶች ለሚካሄዱ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ፈቃድ ይሰጣል፣ ይቆጣጠራል፤
04
የተፈጥሮና ባህላዊ ሃብቶች ጥበቃና አጠቃቀም
የሀገሪቱ የተፈጥሮ ቅርሶች እንዲጠኑ፣ እንዲጠበቁና ለቱሪዝም አመቺ ሆነው እንዲለሙና ጥቅም ላይ እንዲውሉ የሚደረጉበትን ሁኔታ ያመቻቻል፤
05
ተቋማዊ አቅም ግንባታ
አመራርና ሰራተኞች የእውቀት ክህሎትና የአመለካከት ለውጥ በማምጣት፤ሚኒስቴር መ/ቤቱ የተጣለበትን ተቋማዊ ሃላፊነት በብቃት እንዲወጣ የሚያስችሉ በርካታ ሙያዊ ስልጠናዎችን ያዘጋጃል፡፡
ወቅታዊ ዜና

የኢትዮጵያ ማንሰራራት በተግባር ፣ ቢሾፍቱ አየር ማረፊያ ግንባታና የስትራቴጂካዊ ሴክተሮች ቅንጅታዊ ስኬት
የጳጉሜ 2 “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” መሪ ቃልን መነሻ በማድረግ በተካሄደው ሀገራዊ የፓናል ውይይት ላይ ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች የምታስመዘግበው አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገትና የልማት ውጤቶች ተዳሰዋል። በቱሪዝም፣ ማዕድን፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ፣ ከተማ ልማት እንዲሁም

የጳጉሜ 2ን ቀን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል ሀገራዊ ፓናል ውይይት ተካሄድ።
በሀገሪቱ የኢኮኖሚ አዕማድና የዕድገት ምዕራፍን የሚያፋጥኑ አበይት የልማት ዘርፎችና የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ያተኮረ ከፍተኛ የፓናል ውይይት ተካሄደ። በቱሪዝም ሚኒስቴር አስተባባሪነት በተዘጋጀው በዚህ ፓናል መድረክ ላይ በሀገሪቱ እየተመዘገቡ ያሉ የሪፎርም

በሀገሪቱ የተመዘገቡ የልማት ውጤቶችና የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ:-
ጳጉሜ 2 — “የማንሰራራት ቀን”ን በማስመልከት በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች እየተከናወኑ ያሉ እና የተጠናቀቁ ሜጋ ፕሮጀክቶችን የሚያስቃኝ የፎቶ አውደ-ርዕይ ለህዝብ እይታ ቀረበ። አውደ-ርዕዩ በስድስት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችና በስራቸው ስር ባሉ ተቋማት
በቱሪዝም ዘርፍ በቅርብ ዓመታት የተሰሩ መዳረሻዎች ለአገር ገጽታ ግንባታ ከመሆንም በላይ አለም አቀፍ የቱሪዝም መዳረሻ መሆን ችለዋል
መንግስት ባለፉት ዓመታት ለቱሪዝም ዘርፉ በሰጠው ትኩረት የሀገራችንን ጸጋዎች በመረዳት በማልማት፣ በመጠበቅና በመንከባከብ በጠቅላይ ሚኒስቴር ፕሮጅክት ብቻ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ ለምተው በአዲስ መልክ ለጎብኚዎች ክፍት ሆነዋል